የቫይታሚን ዲ (Vitamin D) እጥረት ለስንፈተ-ወሲብ ያጋልጣልን?

የቫይታሚን ዲ እጥረት እጅግ በርካታ ሰዎች ላይ ይከሰታል።ጥናቶች እንደሚያሳዩት የቫይታሚን ዲ እጥረት 50%  የሚሆነውን የአለም ህዝብ ያጠቃል።በተለይም ደግሞ ጥቁር    ሰዎች ላይ በብዛት ይከሰታል ። ይህም የሆነው ጥቁር ቆዳ ከፍተኛ የሜላኒን (melanin) መጠን ስላለውና የፀሐይ ብርሃንን ወደ ውስጥ ስለማያሳልፍ ነው።

ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ቫይታሚን ዲ እጥረት በቀጥታ ስንፈተ -ወሲብን ያመጣል( Cause and effect ) ባይባልም ተጋላጭነትን ግን ይጨምራል  ወይንም ደግሞ ቫይታሚን ዲ እጥረት እና ስንፈተ -ወሲብ ተያያዥነት እንዳላቸው ያሳያሉ። ይህም ማለት አነስተኛ ቫይታሚን ዲ መጠን በደማቸው ውስጥ ያላቸው ሰዎች ለስንፈተ – ወሲብ ተጋላጭ የመሆን ዕድላቸው ከፍተኛ ነው ማለት ነው።

ይህም ብቻ አይደለም አነስተኛ የቫይታሚን ዲ መጠን በደማቸው ውስጥ ያላቸው ሰዎች ለፕሮስቴት ካንሰር ተጋላጭ እንደሆኑም ጥናቶች አመላክተዋል።

በተለይም የደም ውስጥ የቫይታሚን ዲ መጠን ከ20 ng/ml በታች ከሆነ ተጋላጭነቱን በከፍተኛ መጠን ይጨምራል። እጅግ አነስተኛ የቫይታሚን ዲ መጠን ያለው ሰዉ የስንፈት ወሲብ ችግር ካጋጠመው ፣ የቫይታሚን ዲውን መጠን ብቻ በማስተካከል ያለምንም ተጨማሪ መድሀኒት መፈወስ ይችላል ማለት ነው ። ስለሆነም የቫይታሚን ዲን መጠን በላብራቶሪ ምርመራ ማወቅ በጣም አስፈላጊ ነው።

ቫይታሚን ዲን ከሶስት አይነት ነገሮች ማግኘት ይቻላል። ከፀሃይ ብርሃን ፤ ከምግብ እንዲሁም ከመድሃኒት (nutritional supplement) ማግኘት ይቻላል።

በቫይታሚን ዲ የበለፀጉ ምግቦች የሚከተሉት ናቸው። ስብ ያላቸው ዓሣዎች ለምሳሌ salmon fish, tuna , Sardin ፤ እንቁላል ፤  እንጉዳይ (mushroom) እንዲሁም የበሬ ጉበት ናቸው።

በሃኪም የሚታዘዙ በመርፌ ና በሚዋጥ (tablet ) የሚሰጡ መድሃኒቶችም ሲኖሩ እነዚህ በአጭር ጊዜ ውስጥ የቫይታሚን ዲ መጠንን ለማስተካከል ያግዛሉ።

በአጠቃላይ አነስተኛ የ ቫይታሚን ዲ መጠንን በምርመራ በማወቅ እና ተገቢውን ህክምና በመውሰድ  የወሲብ ህይወትን ማሻሻል ይቻላል።

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው